U17 ፕሪሚየር ሊግ ፡ ሲዳማ ቡና እና ሀዋሳ ከተማ ወደ ግማሽ ፍጻሜ ተሸጋግረዋል
ፎቶ ከ ሶከር ኢትዮጵያ የኢትዮጵያ ከ17 አመት በታች ፕሪሚየር ሊግ የማጠቃለያ ውድድር የምድብ ጨዋታዎች ዛሬ ሲጠናቀቁ ሀዋሳ ከተማ እና ሲዳማ ቡና ግማሽ ፍጻሜውን ተቀላቅለዋል፡፡ 10:00 ላይ በወንጂ ሜዳ ጨዋታቸውን ያደረጉት ሐረር ሲቲ እና ሲዳማ ቡና 1-1 አቻ ተለያይተዋል፡፡ ብሩክ ሰሙ ለሐረር ሲቲ ሲያስቆጥር አንለይ የሲዳማ ቡናን ግብ ከመረብ አሳርፏል፡፡ ውጤቱን ተከትሎ ሲዳማ ቡና ነጥቡን 8 በማድረስ የደረጃ ሰንጠረዡ አናት ላይ በመቀመጥ ወደ ግማሸ ፍጻሜው ተቀላቅሏል፡፡ በተመሳሳይ 10:00 አዳማ አበበ ቢቂላ ላይ ቅዱስ ጊዮርጊስ አዲስ አበባ ከተማን ወንድወሰን ቢራራ ባስቆጠረው ግብ 1-0 ቢያሸንፍም ወደ ግማሽ ፍጻሜው ለማለፍ በቂ አልሆነለትም፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከሀዋሳ ከተማ ጋር እኩል 7 ነጥብ ቢይዝም በግብ ልዩነት ተበልጦ ከምድቡ ተሰናብቷል፡፡ የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዎች በመጪው ሀሙስ አዳማ አበበ ቢቂላ ላይ ሲደረጉ 07:00 ላይ ሲዳማ ቡና ከ መከላከያ ፤ 09:00 ላይ አዳማ ከተማ ከ ሀዋሳ ከተማ ይጫወታሉ፡፡ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪዎች 4 ዮሐንስ ደረጄ (መከላከያ) 3 የኋላሸት ፍቃዱ ( አዳማ ከተማ) 3 እንደልቡ ደሴ (ቅዱስ ጊዮርጊስ) 2 ታዲዮስ አዱኛ (ሐረር ሲቲ) 2 ወንድማገኝ ታደሰ (ሀዋሳ ከተማ) 2 ምንተስኖት ማቲዮስ (ሀዋሳ ከተማ) 2 ይገዙ ቦጋለ (ሲዳማ ቡና) 2 ኢሳ ንጉሴ (አዳማ ከተማ) 2 ዳንኤል ጌድዮን (ደደቢት) ምንጭ