በአዲስ አበባ ስታዲየም ይካሄዳል የተባለውና ከሩብ ፍፃሜው እስከ ፍፃሜው ያለው ጨዋታ በሀዋሳ ሊካሄድ እንደሚችል በስፋት እየተነገረ ነው

(ኤፍ.ቢ.ሲ) በ2015ቱ 38ኛው የምስራቅ አና መካከለኛው የእግር ኳስ ውድድር(ሴካፋ) የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ዋልያዎቹ ሩብ ፍጻሜ መቀላቀላቸውን አረጋግጠዋል።
በምድብ አንድ አስተናጋጇ ኢትዮጵያ ከታንዛኒያ አቻዋ ጋር በሀዋሳ ስታዲየም የተጫወተች ሲሆን፥ ውጤቱም 1ለ1 በሆነ አቻ ውጤት ተጠናቋል።
በሴካፋ ዋንጫ ዋልያዎቹ ሩብ ፍጻሜ መቀላቀላቸውን አረጋገጡ
በጨዋታው ታንዛኒያ በ51ኛው ደቂቃ ጎል አስቆጥረው ጨዋታውን መምራት ችለው የነበረ ሲሆን፥ ሙሉ የጨዋታው ሰዓት ተጠናቆ የባከነ ሰዓት ላይ የታንዛኒያ ብሄራዊ ቡድን በራሱ መረብ ላይ ባስቆጠረው ግብ ዋልያዎቹ አቻ በሆነ ውጤት ጨዋታውን አጠናቀው ሊወጡ ችለዋል።
በዚህም መሰረት ዋልያዎቹ ከምድብ አንድ ታንዛኒያ እና ሩዋንዳን ተከትለው በ4 ነጥብ በሶሰተኝነት አጠናቀዋል።
ዋልያዎቹ ምርጥ ሶስተኛ በመሆን ወደ ሩብ ፍጻሜ መቀላቀል መቻላቸውንም አረጋግጠዋል።
በምድብ ሁለት ኡጋንዳ እና ብሩንዲ በሀዋሳ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያካሄዱ ሲሆን፥ ኡጋንዳ ጨዋታውን 1ለ0 በሆነ ውጤት አሸንፋለች።
የ13 ጊዜያት የሴካፋ አሸናፊዋ ኡጋንዳ ወደ ቀጣዩ ዙር ማለፏን አረጋግጣለች።
ከምድብ ሶስት ደቡብ ሱዳን በመጀመሪያ ተሳትፎዋ ወደ ሩብ ፍጻሜ ስታልፍ፥ ማላዊም ደቡብ ሱዳንን ተከትላ  ማለፏን አረጋጣለች።
በተያያዘ በአዲስ አበባ ስታዲየም ይካሄዳል የተባለውና ከሩብ ፍፃሜው እስከ ፍፃሜው ያለው ጨዋታ በሀዋሳ ሊካሄድ እንደሚችል በስፋት እየተነገረ ነው።
ለዚህም የሴካፋ አወዳዳሪ አካላት፣ የውድድሩ ስፖንሰር እና የቴሌቪዥን አስተላላፊው ዲ.ኤስ.ቲቪ እንዲሁም በሀዋሳ የሚገኙት ቡድኖች በከተማውና መስተንግዶው በመደሰታቸው እና ቀሪ ውድድሮች በሀዋሳ እንዲካሄድ ፍላጎት በማሳየታቸው ነው ተብሏል።

Comments

Popular posts from this blog

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ክልል የትግራይ ተወላጆች ምክክር